Wednesday, 21 December 2016

አዕማደ ምሥጢራት



አምድ ማለት ምሶሶ ማለት ነው፡፡ በአምድ የተሠራ ቤት አይዛባም ያለዓምድ የተሠራ ቤት ግን ይፈርሳል አይጸናም፡፡ እንደዚህም ሁሉ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አዕማድ የተባሉ ምሥጢራት ይዞ የተገኘ ሰው ልቡናው በፍቅረ እግዚአብሔር በተስፋ መንግስተ ሰማያት ይጸናል፡፡ እነዚህን አምስቱን እምነታት ሳይዝ የተገኘ ልቡናው በፍቅረ እግዚአብሔር በተስፋ መነንግስተ ሰማያት አይጸናምና አዕማድ ይባላሉ፡፡ስለምን ምሥጢር አላቸው ቢሉ በዓይኔ ካላሣያችሁኝ በእጄ ካላሲዛችሁኝ ብሎ አላምንም አልማርም ይሉ ዘንድ አይገባም በቃል ተምሮ በልቡና ተመራምሮ አዎን ብሎ የሚማሯቸው ስለሆኑ ምሥጢር አላቸው፡፡(ሃይ. አበው ዘአትናትዮስ 14÷ 39 ሃይ. አበው ዘኤራቅሊስ 11÷24 1 ቆሮ 1419 1 ሳሙ 1740)
አምስቱ አዕማደ ምስጢራት የሚባሉት
ጢረ ሥላሴ፡- የምሥጢረ ሥላሴ ነገር እንዴት ነው ቢሉ የሥላሴ አንድነት ሦስትነት ምልዓት ስፋት ርቀት ይህንን ማወቅ ማመን ነው፡፡ (ማቴ 2820) ማወቅ እንደምን ነው ቢሉ ምሥጢሩን መማር ነው ማመንስ እንደምን ነው ቢሉ መናፍቃን ካህናት አላዊያን ነገሥታት ሃይማኖታችሁን ተነስተዉ ፈጣራችሁን ካዱ ለጣዖት ስገዱ ብለው ሰይፍ ስለው እሳት አንድደወ በተነሱ ጊዜ አንክድም ብለው በተማሩት ሃይማኖት ተከራክሮ የደፈረ አንገቱን ለስለት ገላውን ለእሳት ለውግረት ለሞት የፈራ ስደት ይህንን መቀበል ነው፡፡
ስለምን ምሥጢር ተባለ
የሥላሴን አንድነት ሦስትነት በዓይኔ ካላየሁ በእጄ ካልዳሰስኩ አላምንም ይሉ ዘንድ አይገባም በቃል ተምሮ በልቡና ተመራምሮ አዎን ብሎ የሚማሩት የሚቀበሉት ነውና ምሥጢር ተብሏል፡፡
ምሥጢረ ሥጋዌ፡- የምሥጢረ ሥጋዌ ነገር እንደምን ነው ቢሉ ከሦስቱ አካላት ከሥላሴ አንዱ አካል ወልድ በተለየ አካሉ ሰው እንደሆነ ከእግዚእነ ማርያም እንደተወለደ በየጥቂቱ እንዳደገ በሠላሳ ዘመኑ በማየ ዮርዳኖስ በእደ ዮሐንስ እንደተጠመቀ ገዳመ ቆሮንቶስ ገብቶ አርባ መዓልት አርባ ሌሊት እንደጾመ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ሕገ ወንጌልን እንዳስተማረ እንደተሰቀለ እንደሞተ እንደተነሳ በአርባኛው ቀን እንደዐረገ በኋላም ይህችን ዓለም ለማሳለፍ እንደሚመጣ ማወቅ ማመን ነው፡፡(ዮሐ 119)
ስለምን ምሥጢር ተባለ
ረቂቅ መረኮት ርቀቱን ሳይለቅ ከግዙፍ ሥጋ ጋር ተዋሐደ ማለት ሰማይና ምድር የማይችሉት መለኮት ቁመቷ አጭር ወርዷ ጠባብ በሆነ እግዝእትኘ ማርያም ማኅጸን ተቻለ ይህንንም በዓይኔ ካላየሁ በእጄ ካልዳሰስኩ አላምንም ይሉ ዘንድ አይገባም በቃል ተምሮ በልቡና ተመራምሮ አዎን ብሎ የሚማሩት የሚቀበሉት ነውና ምሥጢር ተብሏል፡፡
ምሥጢረ ጥምቀት፡- ስለጌታ እና ስለ ክርስቲያኖች ጥምቀት የምንማርበት ነው (ማር 1616)
ስለምን ምሥጢር ተባለ
ካህኑ ምሥጢረ ጥምቀትን ሲፈጽም አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ብሎ ውሃውን ሲባርከው መንፈስቅዱስ በውሃው ላይ ያድርበታል፡፡ ከጌታችን ቀኝ የወጣው ውሃ ይሆናል(ማየ ገቦ) በዚያ የተጠመቀ ሰው ጸጋ መንፈስ ቅዱስ (ልጅነት) ያገኛል፡፡ ምሥጢሩ ሲፈጸም የሚያይ ወይም የሚጠመቅ ሰው የውሃው ቅዝቃዜ የውሃው ጥቁረት ይታየዋል እንጂ ከሥላሴ ሲወለድ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ ሲያገኝ በዓይነ ሥጋ አይታይም ይህንንም በዓይኔ ካላየሁ በእጄ ካልዳሰስኩ አላምንም ይሉ ዘንድ አይገባም በቃል ተምሮ በልቡና ተመራምሮ አዎን ብሎ የሚማሩት የሚቀበሉት ነውና ምሥጢር ተብሏል፡፡
ምሥጢረ ቁርባን፡- ስለጌታችን መድኃኒታችን አማናዊ ስጋና ደም የምንማርበት (ዮሐ 654)
ስለምን ምሥጢር ተባለ
ካህኑ ምሥጢሩን ሲፈጽም አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ብሎ ኅብስቱን ጽዋውን ሲባርከው ኅብስቱ ተለውጦ ሥጋ አምልክ ወይኑ ተለውጦ ደመ አምላክ የሚሆንበት ምሥጢር ነው፡፡ ይህንን በዓይኔ ካላየሁ በእጄ ካልዳሰስኩ አላምንም ይሉ ዘንድ አይገባም በቃል ተምሮ በልቡና ተመራምሮ አዎን ብሎ የሚማሩት የሚቀበሉት ነውና ምሥጢር ተብሏል፡፡
ጌታ ይህንን ያህል ሥጋውን ደሙን ለምን ሰወረው ቢሉ ቢገልጠው የሚቆርብ የሚያቆርብ አይገኝምና፡፡ እንደምን ቢሉ ኅብስቱ በጻሕል ወይኑን በጽዋ አድርጎ አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስፈኑ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ ላዕሌነ ብሎ ሲባርከው ኅብስቱ ወይኑ ተለውጦ ሥጋ መለኮት ደመ መለኮት ይሆናል እንዴትስ የመለኮት ሥጋ ደም ይፈተታል እንዴትስ ሰው በእሳት ይቀበላል፡፡ ስለዚህም ሰውሮታል፡፡
ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን፡- ስለ ጌታና የሰው ልጆች ትንሣኤ የምንማርበት ናቸው፡፡(ዮሐ 1125)
ስለምን ምሥጢር ተባለ
ይህንንም ምሥጢር በዓይኔ ካላየሁ በእጄ ካልዳሰስኩ አላምንም ይሉ ዘንድ አይገባም በቃል ተምሮ በልቡና ተመራምሮ አዎን ብሎ የሚማሩት የሚቀበሉት ነውና ምሥጢር ተብሏል፡፡
እነዚህን ምሥጢራት ማወቅ መማር እንደአርዮስ ወለድ ፍጡር ነው ከማለት እንደፎጢኖስ የወለድ መገኛው ከእመቤተችን ከተወለደ ወዲህ ነው እንጂ ከዚያ በፊት አልነበረው ከማለት መዓረገ መንግስት እንደሚሰጡ መናፍቃን አብ ንጉሠ ነገሥት ወልድ ቢትትደድ መንፈስ ቅዱስ ብለላቴን ጌታ ነው ከማለት መዓረገ ርቀት እንደሚሰጡ መናፍቃን ከነፍስ ነፍሳት ከነፍሳት መላእክት ይረቃሉ ከመላእእት መንፈስ ቅደስ ይረቃል ከመንፈስ ቅዱስ ወልድ ከወለድ አብ ይረቃል ከማለት በሦስቱ አካላት መካከል ልዩነት እንዳለ ሁሉ እኔ የአብ አገልገጋይ ነኝ ወልድና መንፈሰ ቅዱሰ ለእኔ ምኔ ናቸው እኔ የወለድ አገልጋይ ነኝ አብና ወልድ ምኔ ናቸው እኔ የመንፈስ ቅዱስ ባርያ ነኝ አብና ወለድ ምኔ ናቸው ከማለት ከመናናቃኑ ትምህርት ለመጠበቅ ይረደዳዳል፡፡

No comments:

Post a Comment