Sunday, 8 October 2017

አገልግሎታችንን ከየት እንጀምር?


                    

ጌታችን አምላካችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከዕርገቱ በፊት ሐዋርያትን መንፈስ ቅዱስን እስኪቀበሉ ድረስ ከኢየሩሳሌም እንዳይወጡ እና የተስፋውን ቃል እንዲጠብ አዟቸው ነበር (ሐዋ.1፡4) ግና መንፈስ ቅዱስን ከተቀበላችሁ በኋላ በኢየሩሳሌም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድርም ዳር ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ አለ (ሐዋ.1፡8) እነዚህ ቃላት ከዕርገት በፊት ጌታችን ለመጨረሻ ጊዜ ለሐዋርያት ያዘዛቸው ናቸው፡፡ እስኪ አእዚህ ጋር እንምና ጌታችን የተናገራቸውን እያንዳንዱን ቃላት እናስተውል፤ እነዚህ ለየትኛውም አገልጋይ መርሕ ሊሆኑት ይገባል፡፡ የጌታችን ቃላት  ሳይታሰቡ የተነገሩ እንዳልሆኑ መቼም አንዘነጋውም፡፡ መንፈስ ቅዱስን እስኪቀበሉ  በኢየሩሳሌም ከዛ በይሁዳ እንዲሁም በሰማርያ በመጨረሻም በዓለም ሁሉ እንዲሰብኩ ተናገረ፡፡

በኢየሩሳሌም

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያት ኢየሩሳሌምን ለቅቀው እንዳይወጡና ምስክሩንም በዚያ እንዲጠብቁ ሲያዝዛቸው እናነባለን፡፡ ኢየሩሳሌም ሲል ምን ማለቱ ነው የመጀመርያ ምስክር የምንሆንላት እርሷ ማን ናት ኢየሩሳሌም  የታላቁ ንጉስ ከተማ ናት፤ እንዲሁም የመመስገኛ መቅደሱ የሚገኘባት፡፡ አዎ! ኢየሩሳሌም የጌታችን ማደሪያ የሆነች፤ ቅ/ጳውሎስ  በቤተ መቅደስ እያለ የሚጠራት (1ቆሮ.3፡16) ሊቁ አውግስጢኖስም አንተን እስክታገኝ ድረስ እንዳታርፍ አደረግካት ያላት ልባችን  ናት፡፡ ኢየሩሳሌም ፤ የጌታ የግሉ መኖርያ፡፡ በኢየሩሳሌም ምስክር ትሆኑኛላችሁ ማለት በግል ሕይወታችን እና በራሳችን ምስክር መሆን ማለት ነው፡፡
ብዙዎች ይህንን ቅደም ተከተል እናዛባዋለን፤ ወደ ሰማርያና ወደ ዓለም ዳርቻ እንጓዛለን፡፡በዚህም ብዙ ስህተቶች ይከተሉናል፡፡ የኛ ጌታ ያዘዘን ግን መጀመርያ በኢየሩሳሌም ምስክሮቹ እንድንሆን ነው፡፡ ከኢየሩሳሌም ጥሩ ዜና እንደተገኘ ሁሉ ከእኛም የግል ሕይወት ለሌሎች የሚተርፍ በረከት ይወጣል፡፡
ኢየሩሳሌም የይሁዳ ማዕከል ፣ የቤተ መቅደስ መገኛ መስዋዕቱ የሚቀርብባት ነበረች፡፡ ይህች ብ አይሁዶች ከተለያዩ ሀገራት የምትስብ አእና እረፍትም የምትሰጥ ነበረች፡፡ ልክ እንደዚሁ ኢየሩሳሌም ልባችን፤ መንፈሳዊ ሕይወታችን በብዙ ሰዎች ትታያለች፡፡ በዚህም በአንተ ሰማያዊው አምላክን ያመሰግናሉ፡፡ ስለዚ አንተ የእግዚአብሔር አገልጋይ ሆይ ከውስጠኛው ልብህ (ከኢየሩሳሌም) ምስጋናን መሥዋዕት አድርገህ አቅርብ፡፡
ግን ለምንድን ነው ከኢየሩሳሌም የምንጀምረው ይህች ለጌታችን ምስክር የምንሆንባት ቅርብ ከተማ ናት፡፡ በዚህ በጎ ትሩፋትን ከሰራን ቀደ ውጪ ለመውጣት የበቃን ነን ማለት ነው፤ ምክንያቱም የእግዚአብሔር ኃይል የምንቀበለው ከዚህ ነውና፡፡ ጌታችን ሐዋርያትን የመንፈስ ቅዱስን ኃይል እስኪቀበሉ ድረስ ከኢየሩሳሌም እንዳይወጡ አዟቸዋል፡፡እግዚአብሔር ሁልጊዜ አገልግሎታችን በመንፈስ ቅዱስ ኃይል እንዲከወን ይፈልጋል፤ በዚህም እርሱ ይመሰገናልና፡፡ በራሳችን ጥበብና አቅም ለማገልገል ስንሞክር ስንት ጊዜ በደልን ይሆን ይህ ኃይል ለሐዋርያት የተሰጣቸው በሰገነቱ ላይ (ከምድር ቤት በላይ) ሆነው የአብን የተስፋ ቃል እየጠበቁ በአንድ ልብ ሆነው ሲጸልዩ   ፡ መስኮትና በራቸውንም ዘግተው ስለነበር ነው፡፡(ሐዋ.1፡13) አዎ! በከፍታው ላይ ካልወጣን በስተቀር የመንፈስ ቅዱስን ኃይል መቀበል አይቻለንም፡፡ ይህም ከምድራዊ አስተሳሰብ ከፍ ማለት ፣የነፍስን በርና መስኮት (የስሜት ሕዋሳት) በመዝጋት የአምላካችን ሥራና እና እርዳታ መሻትን ያሳየናል፡፡ በዚህ መንፈሳዊ ሰገነት ላይ ለሐዋርያት ደስታንና ሰላምን ሊሰጣቸው የተገለጠ አምላክ ለእኛም እንዲሁ ይገለጣል፡፡ በዚህ መንፈሳዊ ኃይል ቅ/ጴጥሮስ በአንዲት ደካማ ሴት ፊት የካደውን ኢየሱስ ክርስቶስን ፡ በብዙ ሺ ሰዎች ፊት መሰከረ፤ እኛም በዚህ መንፈሳዊ ኃይል ብቻ አምላካችንን ማገልገል እና በየትኛውም ስፍራ መመስከር ይቻለናል፡፡

በይሁዳ

አይሁዶች የእግዚአብሔር ሕዝቦች የተባሉ፣ ትንቢት የተነገረላቸው፣ እርሱም በሥጋ የተገለጠላቸው እነርሱ ግን ያልተቀበሉት ናቸው፡፡ በይሁዳ ምስክር መሆን ማለት፡ በቤት በቤተሰብ መሐል እንዲሁም በአካባቢያችን ስለ እርሱ መመስከርን ያሳየናል በአብዛኛው ማናችንም ይህን አገልግሎት እንረሳዋለን ፤ ኢያሱ ግን እኔና ቤቴ ግን እግዚአብሔርን እናመልካለን ይላል፡፡ (ኢያሱ 24፡15)
ቅ/ጳውሎስ ደግሞ ነገር ግን ለእርሱ ስለ ሆኑት ይልቁንም ስለቤተሰቦቹ የማያስብ ማንም ቢሆን ሃይማኖትን የካደ ከማያምን ሰው ይልቅ የሚከፋ ነው፡፡  (1ጢሞ.5፡8) አዎ! ሐዋርያው እውነተኛ አገልጋይ የሚመዘነው  በቤቱ ባለው ማንነት ነው  እያለ ያስረግጥልናል፡፡ስለቤተሰቡ የማያስብ እንዴት ስለእግዚአብሔር እጨነቃለሁ ይላል በእውነት ይህስ የመታየት ፍላጎት አይመስላችሁም

በሰማርያ

ሰማርያ የአይሁድ እና የአህዛብ ድብልቅ የሆነች ከተማ ናት፡፡ በዚህ የሚደረግ አገልግሎት በሃይማኖት ባሉና በማያምኑ መካከል የሚኖርን ምስክርነት ያሳየና ፡፡ በእውነተኛ ማንነቱ እንዲሁም በቤተሰቡ መካከል የክስቶስን ፍቅር የገለጠ አገልጋይ ብዙ ዝግጅት እና ተጋድሎ ወደሚጠይቀው የመንፈሳዊ ትግል ሜዳ ይገባል፡፡ በሰማርያ ማገልገል ፍቅርን ፣ ምሕረትን እንዲሁም ስለሌሎች መጨነቅን ይፈልጋል፡፡ መንፈሳዊውን ኃይል ሳይቀበሉ በፊት ወደዚህች ከተማ የገቡ ፍቁረ እግዚእ ዮሐንስና ወንድሙ ያዕቆብ ከተማዋ የጌታን ቃል ስላልተቀበለች እሳት ከሰማይ ወርዶ ሰዎቹን እንዲበላቸው ለምነው ነበር ፤ እርሱም ይህን ስጋዊ መንፈስ በመቃወም እንዲህ አላቸው ምን ዓይነት መነፈስ እንደሆነላችሁ አታቁም የሰው ልጅ የሰውን ነፍስ ሊያድን እንጂ ሊያጠፋ አልመጣም አላቸው፡፡ (ሉዋ9፡51-56)
አገልጋይ በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ ውስጥ ለማገልገል የተለየ መንፈሳዊ አቅም ያስፈልገዋል፡፡ ይህ ከባድ የአገልግሎት ሜዳ ቢሆንም አንድ በእምነት የሆነ ለብዙዎች እንደሚተርፉ በዮሐንስ ወንጌል ያለችው ሳምራዊቷ ሴት ጠንካራ ማስረጃችን ናት፡፡ (ዮሐ.4፡6)

እስከ ዓለም ዳርም ድረስ

የጌታችን ወንጌል በየቦታው ሲነገር ማየትን የመሰለ ምን ደስታ አለ፡፡መልካሙ የምሰራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው፡፡ (ሮሜ.10፡15) ምንም በማያውቃቸው ሰዎች መሐል፤ ወገኖቼ አሉልኝ በማይባልበት ስፍራ፣ በቋንቋ እና መልክ ፣ በባህልና በሥርዓት በማይተሳሰርባቸው አካባቢዎች የጌታን ቃል የፍቅርን ኃይል ተሸክሞ መጓዝ ምንኛ ያስደስታል፤ እንዴት ያለ መባረክ ነው!
አምላኩን መስሎ ስለእርሱ በፍቅር የሞተለትን እያሰበ ለሰይጣን እንኳን ንስሐ የለመኑትን እነ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራን በዓይነ ኅሊናው እየሳለ የፍቅርን ደሞዝ ለመቀበል የሚጓዝ እውነተኛ አገልጋይ ይህ ነው፡፡
በእርግጥ እነዚህ ሁሉ የተለየ ስብዕና ይፈልጋሉ ፤ እምነት እና እርጋታን ያስቀድማሉ፡፡ በሃይማኖትን መኖርን የክርስቶስን ትእዛዝ መከተልን አጥብቀው ይሻሉ፡፡


ምንጭ፡- Paradise of the spiritual service
 (By Bishop Youhanis )

1 comment: