Saturday, 24 June 2017

‹‹ሚድያና የክርስትና ሕይወት በትውልዱ መካከል›› ክፍል አራት የመጨረሻ ክፍል

  

ዳዊት ደስታ
/dawitdesta126@gmail.com/

በሶሻል ሚድያ ‹‹ሚድያና የክርስትና ሕይወት በትውልዱ መካከል›› በሚል በተከታታይ ሦስት ክፍል እያሳደረ ያለውን ጽዕኖ በወፍ በረር አስቃኝቻቹ ነበር፡፤በዚህ በመጨረሻው ጽሑፌ ላይ በትውልዱ ላይ ያጠላውን ጥላ ተመልክተን የመፍትሄ አካል እንድንሆን ችግሩን በጥቂቱ እነሆ፡፡አስተያየትና ጥያቄ ለመቀበል ዝግጁ ነኝ ዳዊት ብላችሁ ጻፉልኝ፡፡

ትውልዱ ላይ የሚፈጥሩት የስነ ምግባር፣የባህሪ ችግር


4 አስርት አመታት በዘለቀው የቴሌቪዥን ተጽእኖ ላይ ትኩረቱን ያደረገ የጥናት ሪፖርት እንደሚያመለክተው በአማካይ ‹‹በሰአት እስከ 50 ወንጀሎችና ከደርዘን በላይ የሚደርሱ የነፍስ ግድያዎች በምእራባውያን ቴሌቪዥን ፕሮግራሞች ይታያሉ፡፡ በዚህ ስሌት መሰረት አንድ ሰው 17 አመት እድሜ ላይ ሲደርስ 800 እስከ 1.5 ሚሊዮን የሚደርሱ የጭካኔ ድርጊቶችና ከሩብ ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ነፍስ ግድያዎችን ይመለከታል›› ማለት ነው፡፡በሚል ተዘግቦል፡፡ይሄንን አሁን ካለው የሚድያ ሁኔታ ትውልዱ ላይ እየተጫነ ያለው ነገር ምን እንደሆነ እንድንረዳ ያደርገናል፡፡
ቴክኖሎጂው መስፋፋት
በሁለት ቀናቶች ውስጥ ብቻ ከአንድ መቶ አስር ሺህ በላይ የሚሆኑ የፌስቡክ ተጠቃሚዎችማግኔትበሚባል ትሮጃን ቫይረስ ተጠቅተዋል፡፡ቁጥሩ እጅጉን እየጨመረ ይገኛል፡፡ ይህ ቫይረስ የሚያደርገው በቫይረሱ የተጠቃውን የፌስቡክ ተጠቃሚና የርሱ ጓደኞችን ታግ(tag) በማድረግ መጥፎ ምስሎችን(pornography) ወይም ራቆታቸው የሆኑ የወንድና ሴት ምስሎችን ፖስት ያደርጋል፡፡/http://goo.gl/eKTrkJ Source: https://
በአሁኑ ወቅት በዓለም 1ነጥብ 5 ቢሊዮን ሕዝብ በላይ የፌስ ቡክ ተጠቃሚ አለው ይባላል። በአፍሪካ ደግሞ የተጠቃሚው ቁጥር ወደ 125 ሚሊዮን እንደሚጠጋ ኢንተርናሽናል ወርልድ ስታተስ የተሰኘ ድረ ገፅ ላይ የሰፈር መረጃ ያመለክታል።ወጣቱ በዘመናዊ ስልኩን በመጠቀም፤ ሲበላ ፌስ ቡክ፣ ሲተኛም ፌስ ቡክ፣ መንገድ ሲሄድ ፌስ ቡክ፣ ካፌ ሲቀመጥ ፌስ ቡክ ሆኗል ተግባሩ። ምን ወጣቱ ብቻ፤ ጎልማሳው፣ ሴቱ፣ ታዳጊዎችና አንጋፋውም ጭምር እንጂ።‹‹ማኀበራዊ ድረ ገጽ ምንነት ጥቅምና ጉዳት›› በሚል በሠራሁት ጥናት መረጃ ለመሰብሰብ 110 የሚሆኑ የትራንስፖርት ምልልስ ሳደርግ የታዘብኩት በአንድ ታክሲ ውስጥ 3-5 ሰው ስልኩን አውጥቶ ፌስ ቡክ፣ጌምና ሌሎችንም ነገሮች እየተጠቀመ እንዳለ ተረድቻለው፡፡
በአሁኑ ሰዓት በፌስ ቡክ (Facebook) ላይ በግለሰቦች ስም፣በሕብረት ስም (Group)Public figureCommunity በማድረግ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ስም አካውንት በመክፈት በመረጃ መረቦች (Internet) ላይ ብሎጎችን (blogs) በኦርቶዶክስ ተዋህዶ አባቶችና ቅዱሳን፣ ሊቃውንት፣ ጳጳሳት ስም የተለያዩ ድኅረ ገጾችን በመክፈት የመናፍቃንን የክህደት ትምህርት የሚያሰራጩ በዝተዋል፡፡በኦርቶዶክስ ስም የሚጻፉት ሁሉ የቤተክርስቲያናችን ትምህርት አለመሆኑን አውቀን ራሳችንን ከኑፋቄ መጠበቅ ይኖርብናል፡፡

ትውልዱ ላይ እየፈጠሩት ያለው የሞራል መላሸቅ


የሞራል መላሸቅ የምህራቡ ዓለም የፕሮቴስታንቱ አስተሳሰብ ትውልዱ ላይ እያሳደረ ያለው ማጠልሸት ምልክት ነው፡፡
ተጠናቀቀ
ስብሐት ለእግዚአብሔር

‹‹ሚድያና የክርስትና ሕይወት በትውልዱ መካከል›› ሦስተኛ ክፍል


                                                                                 ዳዊት ደስታ
/dawitdesta126@gmail.com/
በተከታታይ ሚድያና የክርስትና ሕይወት በሚል ርዕስ ትውልዱ ላይ እያሳደረ ያለውን ተጽዕኖ እያቀረብኩላችሁ ነበር፡፡ለዛሬ ደግሞ ዘመናዊ ስልኮች፣በሆሊውድ የሚለቀቁልን ዘፈኖች ክርስትናው ላይ ጥላሸት የመቀባት ሥራ እየተሠራ እንደሆነ እንድናውቅና የቤት ሥራችንን እንድንሠራ ይህንን መልዕክት በመረጃ የተደገፈ ጽሑፎችን በፌስ ቡክ ስለቅ ለሶስተኛ ጊዜ ነው፡፡ይቀጥላል አስተያየትና ጥያቄዎች ካላችሁ ኢሜል ያድርጉልኝ፡፡

ዘመናዊ ስልኮች

ዘመናዊ ስልኮችን (smart phone)መግዛትና መጠቀም ከጊዜ ወደ ጊዜ በብዛት እየጨመረ ይገኛል::ጥናቶች እንደሚያመለክቱት ከሆነ ስልክ እየተጠቀሙ መተኛት ወይም ደግሞ ከመኝታ አንድ ሰዓት በፊት ዘመናዊ ስልኮችን መጠቀም በሀይለኛው የእንቅልፍ ጥራትን እንዲሁም ባጠቃላይ ጤንነትን ዘላቂ በሆነ ሁኔታ ይጎዳል::በቂ እንቅልፍ አገኘንም አላገኘን ከመተኛታችን አንድ ሰዓት በፊት ዘመናዊ ስልኮቻችንን የምንጠቀም ከሆነ አእምሯችን "ሜላቶኒን" የተሰኘውን ሆርሞን ከማመንጨት ይታቀባል::ይህ ሆርሞን እንቅልፍ መተኛት ሲያስፈልገን ለሰውነታችን አስፈላጊውን ምልክቶች የሚያስተላልፍ ነው::
የዚህ ሆርሞን አለመመረት ወይም በበቂ ሁኔታ አለመገኘት ታዲያ ለተለያዩ የጤና ችግሮች ያጋልጣል::
የእንቅልፍ ሰዓት ማነስ
የማስታወስ አቅም መቀነስ
የደከመ እንቅስቃሴ (reflex)
አላስፈላጊ ውፍረት
ከባድ የሆነ ድብርት እና በስተመጨረሻም
ለካንሰር በሽታ ሊያጋልጠን ይችላል::
በመሆኑም ከመተኛታችን አንድ ሰዓት በፊት ስልካችንን መጠቀም ማቆም ብንችል የተመረጠ ይሆናል::ምንጭ: http://wonderfulengineering.com

የሆሊውድ ዘፈኖች

በሙዚቃው ኢንዲስትሪ ውስጥ ለምሳሌ“Stairway to Heaven” በሮክ ዘፈን ታሪክ በጣም ከተሰሙና በኤፍ ኤም ሬዲዮኖች በብዛት ከተደመጡ ዘፈኖች አንዱ ነው፡፡ በሃይማኖት ሽፋን የዝሙት አስተሳሰብ የሚያነሳሳ ነው፡፡
• “ጎትስ ሄድ ሱፕየፍየል ራስ ሾርባ 1973 የሙዚቃ አልበም “Sympthy for the devil፤ሲምፒቲ ፎር ዘዴቭልየተሰኘው ሙዚያ የሠይጣን ማምለኪያ ቦታ ለሆነው መዝሙሮች አንዱ ነው፡፡
2005 .. የተደረገ አንድ ጥናት እንደሚያመለክተው እድሜያቸው 14-35 ዓመት የሚሆኑ ወጣቶች Pornography ህይወት ከመጠመዳቸው በፊት 78% የሚሆኑት ከዘፈን ጋር ልዩ ወዳጅነት እንደነበራቸው ጥናቱ ጠቁሞል፡፡
666 የቀንድ ምልክት፣ የሦስት ጎን በአንድ አይን ምልክቶች በብዙ ፊልሞች ላይ እያየን ነው፡፡
• Hymn to Lucifer(ለዲያብሎስ ውዳሴ) ይገባል በሚል /Alcister crowley/ዘፍኖአል፡፡ ሌዲ ጋጋ2009 MTV VMA የአዋርድ ዝግጅት ሽልማቷን በተቀበለችበት ወቅት “Thanks for God and for gays” ብላለች፡፡
ክርስትናን ማንቆሸሽ

በምራቡ ዓለም ጸረ ክርስትና የክርስቲያኖችን አስተምህሮና የአምልኮት መገለጫዎችን ለማንቋሸሽ፣ ጭቃ ለመቀባትና ለማስነወር የመዝናኛ ኢንዱስትሪው ለሕጻናት የሚዘጋጁ ፊልሞችን እንኳ ከመጠቀም ወደ ኋላ አላሉም፡፡የክርስትና አስተምህሮዎችን፣ ቀኖናዎችን፣ ባህላዊና ትውፊታዊ እሴቶችን እንዲሁም ግብረገባዊ መርሆዎችን የሚተቹና የሚያንቋሽሹ መምጣት ለትውልዱ ትልቅ ፈተና ነው፡፡



ክርስቲያኖችን ደም የጠማቸውና ስለ ስልጣኔ አንዳችም ግንዛቤ የሌላቸው ቡትቶ ለባሽ ደንቆሮዎች አድረጎ የሚስለው ‹‹አጎራ›› የክርስቲያን ምእመናን እንደ ወሮበሎች ቤተመጻሕፍትን ሲያፈርሱ፣ መጻሕፍትን ሲያቃጥሉ፣ ፈላስፎችና ተመራማሪዎችን በሐይማኖት ስም ሲጨፈጭፉ ያሳያል፡፡
በዚህ የሙዚቃ ቪዲዮ ላይ ክርስቶስና ደቀመዛሙርቱ ሐዋርያት ሞተር ሳይክል እንደሚነዱ ጋንግስታሮች ተደርገው ቀርበዋልሌዲ ጋጋም ሴተኛ አዳሪ ሊያስመስላት በሚችል መልኩ ተቀርጻ ክርስቶስን እንዲወክል ካስቀመጡት ሰው ጀርባ ተቀምጣትታያለች (ይህም ሆሊውድ እያቀነቀነው የሚገኘውክርስቶስና ማርያም መግደላዊት ጾታዊ ግንኙነት ነበራቸው የሚለው ስድብ አካል ነው)
በአጠቃላይ የክርስትናን አስተምህሮ ከሚያንቋሽሹ፣ በመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችና በቅዱሳን አባቶች ላይ ከሚያላግጡ ፊልሞችና የሙዚቃ ቪዲዮዎች መካከል እጅግ ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
                                                                                                                                     ይቀጥላል፡፡


                                                                                                      ስብሐት ለእግዚአብሔር