Saturday, 24 June 2017

‹‹ሚድያና የክርስትና ሕይወት በትውልዱ መካከል›› ክፍል አራት የመጨረሻ ክፍል

  

ዳዊት ደስታ
/dawitdesta126@gmail.com/

በሶሻል ሚድያ ‹‹ሚድያና የክርስትና ሕይወት በትውልዱ መካከል›› በሚል በተከታታይ ሦስት ክፍል እያሳደረ ያለውን ጽዕኖ በወፍ በረር አስቃኝቻቹ ነበር፡፤በዚህ በመጨረሻው ጽሑፌ ላይ በትውልዱ ላይ ያጠላውን ጥላ ተመልክተን የመፍትሄ አካል እንድንሆን ችግሩን በጥቂቱ እነሆ፡፡አስተያየትና ጥያቄ ለመቀበል ዝግጁ ነኝ ዳዊት ብላችሁ ጻፉልኝ፡፡

ትውልዱ ላይ የሚፈጥሩት የስነ ምግባር፣የባህሪ ችግር


4 አስርት አመታት በዘለቀው የቴሌቪዥን ተጽእኖ ላይ ትኩረቱን ያደረገ የጥናት ሪፖርት እንደሚያመለክተው በአማካይ ‹‹በሰአት እስከ 50 ወንጀሎችና ከደርዘን በላይ የሚደርሱ የነፍስ ግድያዎች በምእራባውያን ቴሌቪዥን ፕሮግራሞች ይታያሉ፡፡ በዚህ ስሌት መሰረት አንድ ሰው 17 አመት እድሜ ላይ ሲደርስ 800 እስከ 1.5 ሚሊዮን የሚደርሱ የጭካኔ ድርጊቶችና ከሩብ ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ነፍስ ግድያዎችን ይመለከታል›› ማለት ነው፡፡በሚል ተዘግቦል፡፡ይሄንን አሁን ካለው የሚድያ ሁኔታ ትውልዱ ላይ እየተጫነ ያለው ነገር ምን እንደሆነ እንድንረዳ ያደርገናል፡፡
ቴክኖሎጂው መስፋፋት
በሁለት ቀናቶች ውስጥ ብቻ ከአንድ መቶ አስር ሺህ በላይ የሚሆኑ የፌስቡክ ተጠቃሚዎችማግኔትበሚባል ትሮጃን ቫይረስ ተጠቅተዋል፡፡ቁጥሩ እጅጉን እየጨመረ ይገኛል፡፡ ይህ ቫይረስ የሚያደርገው በቫይረሱ የተጠቃውን የፌስቡክ ተጠቃሚና የርሱ ጓደኞችን ታግ(tag) በማድረግ መጥፎ ምስሎችን(pornography) ወይም ራቆታቸው የሆኑ የወንድና ሴት ምስሎችን ፖስት ያደርጋል፡፡/http://goo.gl/eKTrkJ Source: https://
በአሁኑ ወቅት በዓለም 1ነጥብ 5 ቢሊዮን ሕዝብ በላይ የፌስ ቡክ ተጠቃሚ አለው ይባላል። በአፍሪካ ደግሞ የተጠቃሚው ቁጥር ወደ 125 ሚሊዮን እንደሚጠጋ ኢንተርናሽናል ወርልድ ስታተስ የተሰኘ ድረ ገፅ ላይ የሰፈር መረጃ ያመለክታል።ወጣቱ በዘመናዊ ስልኩን በመጠቀም፤ ሲበላ ፌስ ቡክ፣ ሲተኛም ፌስ ቡክ፣ መንገድ ሲሄድ ፌስ ቡክ፣ ካፌ ሲቀመጥ ፌስ ቡክ ሆኗል ተግባሩ። ምን ወጣቱ ብቻ፤ ጎልማሳው፣ ሴቱ፣ ታዳጊዎችና አንጋፋውም ጭምር እንጂ።‹‹ማኀበራዊ ድረ ገጽ ምንነት ጥቅምና ጉዳት›› በሚል በሠራሁት ጥናት መረጃ ለመሰብሰብ 110 የሚሆኑ የትራንስፖርት ምልልስ ሳደርግ የታዘብኩት በአንድ ታክሲ ውስጥ 3-5 ሰው ስልኩን አውጥቶ ፌስ ቡክ፣ጌምና ሌሎችንም ነገሮች እየተጠቀመ እንዳለ ተረድቻለው፡፡
በአሁኑ ሰዓት በፌስ ቡክ (Facebook) ላይ በግለሰቦች ስም፣በሕብረት ስም (Group)Public figureCommunity በማድረግ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ስም አካውንት በመክፈት በመረጃ መረቦች (Internet) ላይ ብሎጎችን (blogs) በኦርቶዶክስ ተዋህዶ አባቶችና ቅዱሳን፣ ሊቃውንት፣ ጳጳሳት ስም የተለያዩ ድኅረ ገጾችን በመክፈት የመናፍቃንን የክህደት ትምህርት የሚያሰራጩ በዝተዋል፡፡በኦርቶዶክስ ስም የሚጻፉት ሁሉ የቤተክርስቲያናችን ትምህርት አለመሆኑን አውቀን ራሳችንን ከኑፋቄ መጠበቅ ይኖርብናል፡፡

ትውልዱ ላይ እየፈጠሩት ያለው የሞራል መላሸቅ


የሞራል መላሸቅ የምህራቡ ዓለም የፕሮቴስታንቱ አስተሳሰብ ትውልዱ ላይ እያሳደረ ያለው ማጠልሸት ምልክት ነው፡፡
ተጠናቀቀ
ስብሐት ለእግዚአብሔር

No comments:

Post a Comment