የካቶሊካዊያን ብቻ የሚቀበሏቸው ጉባኤያት
ጉባኤ ላተራን የመጀመርያው
የቤተ
ክርስቲያኒቱ መሪ በራሱ ሥልጣን ጳጳሳትን ይሾም ዘንድ ከመንግስትም ጋር በሕብረት እንዲሰሩ የተወሰነበት ጉባኤ ነው፡፡ ይህ ጉባኤ
መሠረተ እምነት ላይ የተመረኮዘ ጉባኤ አይደልም፡፡ ተጨማሪ 25 ቀኖናዎችና ድንጋጌዎች በዚህ ጉባኤ ላይ ተሰርተዋል፡፡
ጉባኤ ላተራን የሁለተኛ
ይህም
ስለካህናት የጋብቻ ሁኔታ ስለዲያቆናትና ስለመነኮሳት የአኗኗር ሥርዓት ቀኖና የተሰራበት ነው፡፡ ቀሳውስትና መነኮሳት በድንግልና
ሕይወት መኖር እንደሚገባቸው ካቶሊካዊያኑ የወሰኑት በዚህ ጉባኤ ነበር፡፡ ይህ ቀኖና ከጥንታዊያን ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት
ልዩ የሆነ ነው ምክንያቱም ቀሳውስት ሕጋዊያን ጭምር መሆን ይችላሉና ነው፡፡ ተጨማሪ 30 ቀኖናዎችና ድንጋጌዎች በዚህ ጉባኤ ላይ
ተሰርተዋል፡፡
ጉባኤ ላተራን የሦስተኛ
የፖፕ
አመራረጥ ሥርዓትን በተመለከተ ቀኖና የተሰራበት ነው፡፡ ፖፑ የጉባኤውን ሁለት ሦስተኛ ድምጽ አግኝቶ መመረጥ እንዳለበት ይደነግጋል
ይህም ሥርዓት እስከ ፖፕ ጆን ፖል ሁለተኛ ድረስ የተሰራበት ነው፡፡በገንዘብ ክህነትን ስመቀበል ሲሞናዊነትና ስለሕገወጥ የመሳሪያ
ሽያጭ በዚህ ሙስሊሙን መርዳት በሚመለከትም ውሳኔ አሳልፎል፡፡
ጉባኤ ላተራን የአራተኛ
በዚህ
ጉባኤ ቢያንስ የእምነቱ ተከታይ የሆነ ሰው በትንሣኤ ንስሐን እንዲቀበልና ቁርባን አንዲቆርብ የተደነገገበት ነው፡፡ቁርባን መታሰቢያ
እንደሆነም የወሰኑት በዚህ ጉባኤ ነው፡፡[1]
የመጀመርያው ለዩን
ይህ
ጉባኤ የተለየ ውሳኔ ያላሳለፈ ጉባኤ ስሆን በዚህ ጉባኤ ላይ ከስፔን ከፈረንሳይ ከጣሊያን ግዛት ብቻ የተወጣጡ የካቶሊክ አባቶች
እንደተሳተፉ ይነገራል ይህም የሆነበት ምክንያት በወቅቱ በነበረው የፖለቲካ ችግን ልዩን የጀርመን ግዛት ተዘግታ በንጉሡ ፉሬድሪክ
ሁለተኛ ተዘግታ ስለነበር ነው፡፡በጉባኤው 22 ምዕራፍ ያካተተ ውሳኔ ተላልፉል፡፡
በዚህ
ጉባኤ ላይ ከግሪክቤተ ከርስቲያን ጋር በመስማማት ወደ ቀደመ አንድነታቸው ለመምጣት ጥረት የተደረገበት ነው፡፡ ነገር ግን በወቅቱ
የነበሩት ነገሥታት በማስፈራራት በስምንት ቀናት ውስጥ የፖፑን ሐሳብ እንዲቀበሉ ግድ አሏቸው፡፡ ግሪክ ቤተ ክርስቲያንም የተወከሉ
አባቶች ይህንን አልቀበልም በማለታቸው እንደቀድሞ እስካሁንም ድረስ ተለያይተው ይኖራሉ፡፡
በዚህ
ጉባኤ ላይ ፖፕ ቀለሜንጦስ አራተኛ ከተለያዩ ሃገራት የተወጣጡ ጳጳሳት ቅሬታቸውን እንዲያቀርቡ ካደረገ በኃላ አስተዳደራዊ ጥያቄዎች
ላይ መልስ የሰጠበት ጉባኤ ነው፡፡ አስተዳደራዊ ችግሮች ተብለው ከተነሱት መካከል የጳጳሳት አስተዳደራዊ ነጻነት ነበር ይህንም ለመፍታት
በጉባኤው ተማክረዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ክርስትናን ለማስፋፋትና እስልምና መስፋፋትን በተመለከተ ጉባኤው መክሮል፡፡
ጉባኤ ኮንስታንስ ባሰል ፋራር ፍሎራንስ
ይህ
ጉበኤ ስለሰው ነፍስ ዘለዓለማዊነት የተወሰነበት ጉባኤ ነው፡፡ ካቶሊካዊያኑ ስለሰው ነፍስ ያላቸው አቋም ምን እንደሚመስል ማሳወቁ
እዚህ ጋር ጠቃሚ ሳይሆን አይቀርም አንዲህ የምናሊ ‹‹Every spiritual soul is created immediately
by God-it is not <> by the parents>> በማለት ለእያንዳንዱ ጽንስ
አዲስ ነፍስ ወዲያውኑ እንደሚፈጠርላት ያስተምራሉ፡፡ creationism የሚባለው አስተምሕሮ ይህ ነው፡፡
የመንፍቅንኑን
በስም ሳይጠቀስ ይህን ውሳኔ አሳልፏል ‹‹ሰዎች በቅድስና መለወጥ ይገባቸዋል እንጂ ቅድስና በሰዎች አይለወጥም››[2] የሚል ጉባኤው ሌሎች የቀኖና ማሻሻዎችን አድርጓል፡፡
ጉባኤ
ተረንት
ይህ ጉባኤ
ምንፍቅናን ለማውገዝ የተሰነበሰበ አይደለም፡፡ በወቅታዊ ሁኔታች ላይ ተወያይቶ ውሳኔውን ያሳልፏል፡፡ከሌሎች የክርስትና ክፍሎች
ጋር ሊኖር ስለሚገባው ግንኙነት ስለቅዱሳት መጻሕፍት እና ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ተወያይቷል፡፡
በዚህ ጉባኤ 1870 ዓ.ም. ቫቲካን አንድ ጉባኤ ላይ
የተወሰነው ፖፑ ፍጹም አይሳሳትም የሚለውን ሐሳብ በዚህ ጉባኤ ተነስቶ ዳግመኛ አጽንተውታል፡፡
ለጥንታዊያን ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ማለትም እስክንድርያ(ኢትዮጵያና
ኤርትራን ይጨምራል) ሶርያ ሕንድና አርመን የጉባኤውን ሐሳብ በመቃወም በኃይልና በማስፈራራት ከጉባኤው እንዲወጡ በመሆኑ
ለአብያተ ክርስቲያናቱ መለያየት ምክንያት ሆኖል
2. ጉባኤ ቁስጥንጥንዩስ አራተኛ
ይህ ጉባኤ ለሁለቱ ቤተ ክርስቲያን ክፍፍል መፈጠር እንደመነሻ
የሚታይ ነው ይህም በዚህ ጉባኤ ላይ የተነሳው የመንፈስ ቅዱስ ከአብና ከወልድ የሰረጸ ነው የሚለው ትምህርት ነው ይህ ትምህርት
ከዚህ በፊት ያልነበረ ስርዋጽ ነውና ይህን በመቃወም የምሥራቅ አብያተ ክርስቲያናት የሮም ቤተ ክርስቲያን ፖፕን ወቀሱ መናፍቅ ነህም
አሉ፡፡ በዚህም ምክንያት ጉባኤው ተደረገ የሮም ቤተ ክርስቲያን መሪ ነችና የእኛ ሐሳብ ያደመጥ አለች ይህንን ምሥራቃውያን ተቃወሙት
ፓፕ ኒኮላስም በዚህ ጉባኤ ላይ የስሕተት ትምህርቱን አጸደቀው፡፡ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን እስካሁን ድረስ ዘሰረጸ እምአብ ወእም
ወልድ ብለው ያስተምራሉ፡፡
ጉባኤው የተደረገበት ዘመን
|
ጉባኤ
|
የጉባኤው መግለጫ
|
የጉባኤውን ውሳኔ ተከትሎ
|
451
|
ኬልቄዶን
|
ምንታዌ
|
ጥንታዊያን አብያተ ክርስቲያናት
|
870
|
አራተኛው ቁስጥንጥንያ
|
መንፈስቅዱስ ከአብና ከወልድ የሚሰርጽ
መሆኑ የወሰነበት ጉባኤ[3]
|
የምዕራብ አብያተ ክርስቲያናት
|
መለካዊያኑ በቅድመ ስማቸው የቀጠሉ ሲሆን በ1054 ዓ.ም. ከምዕራባዊያኑ
ካቶሊካዊያን ተገንጥለዋል፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት በዋነኝነት ካቶሊካዊያኑ መንፈስ ቅዱስ ከአብና ከወልድ የሰረጸ ነው የሚለውን
ትምህርት በማስተማራቸው ይህንንም የቁስጥንጥንያ ቤተ ክርስቲያን በመቃወሟ ነው፡፡ ነገር ግን እስካሁን ድረስ ሁሉት ባሕርይ የሚለውን
ትምህርት የሚቀበሉ በመሆናቸው ከጥንት ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት በመሠረተ እምነት ደረጃ ልዩ ብያደርገንም በነገረ መለኮት
አረዳድ ባሕል ግን በብዙ የምንቀራረብ ነን፡፡
[1] The Council formally repeated
Catholic teaching, that Christ is present in the Eucharist and thus clarified transubstantiation.
[2] People must be transformed by holiness not
holiness by the pepole
[3] Pop Nicholas l say I had refused to
recognize Patriarch I of Constantinople who attached the pop as a
heretic.because the pop teach the concept of Filioque(holy sprit emanating from
God the father and the son
No comments:
Post a Comment